ላኼም - ነፍሥንና እውቀትን መመገብ

ማሕበረሰባዊ የቋንቋ፣ የጤናና የመንፈሣዊ ትምህርት መስጫ ማዕከል

በመንፈሣዊ በኩል

የኦሪት እምነት፣ ቅርስና ትውፊት ጥልቅ እውቀት። ከዋናው ምንጭ ጋር በማገናኘት የማሕበረሰብ ማንነትን የሚያጠናክሩ ትምህርቶች፣ ቪዲዮዎችና ግብዓቶች።

በሕክምና በኩል

በማሕበረሰቡ ውስጥ ጤናን በሚገባ ለመረዳትና ለማሻሻል አስፈላጊ የሆኑ የሕክምና መረጃዎችን፣ ቀላል ማብራሪያዎችንና የሕክምና ሰነዶችን ትርጉም ማቅረብ።

በቋንቋ በኩል

በፅንሰ-ሐሣብ ላይ የተመሠረተ የቋንቋ ትምህርት- ዕብራይስጥ፣ አማርኛና ግእዝ። የባህል ክፍተቶችን በማጥበብ በትውልድ መካከል ያሉ ግንኙነቶችን ለማጠናከር የሚያስችሉ ለሁሉም ደረጃዎች የሚውሉ የኦንላይን ትምህርቶችና ቪዲዮዎች።

ቀጣዩ ትምህርት፦

ኦንላይን የቋንቋ ሥልጠና

ከተለመደው የማስተማርያ ዘዴ ለየት ባለ መልክ በሁሉም ኢትዮጵያዊ ዘንድ የሚታዎቁትን የአማርኛ ፊደላት ቅርጽና ሥርዎ ቃላት ብቻ በመጠቀም እብራይስጥን ለመማር ቀላል በሆነ ቀመር መጥኖ ስለሚያስተምር ላኼም ተመራጭና በአጭር ጊዜ ውስጥ ውጤታማ እንዲሆኑ ያደርግዎታል። ክፍሉ ከቋንቋውም በላይ ተግባራዊ ምልከታዎችንና እሥራኤላዊነትን ለማስተማር እውነተኛ የሕይወት ተኮር ምሣሌዎችን በውስጡ ያቀፈ ነው።

በላይቭ ይቀላቀሉን!

እሑድ

17:00

በዙም

ስለ እኛ በጥቂቱ

ላኼም የሚለው ቃል በዕብራይስጥ “ለእርሥዎ” የሚል ትርጉምን ያዘለ ሲሆን በጤና፣ አስተዳደርና ኦሪት ላይ ያለንን ጽንሰ ሐሣብ ከሌላው ዓለም ጋር ለማካፈል የምንወድበት መፍትሔ ተኮር የማስተማሪያ ድረ ገጽ ነው። ራእያችን በ2030 ሠላማዊ፣ ተደማጭነት ያለው፣ ጤናማና መፍትሔ ያለውን ትውልድ መፍጠር ነው። የቅርብ ጊዜ ፕሮጀክቶቻችንን በማየት እንደሚደሰቱ ተስፋ እናደርጋለን – ለግብረመልስዎ ወይም ላሠቡት ማንኛውም ትብብር ሊያገኙን ይችላሉ።

የሕክምና ሠነዶችን ቀለል ባለ ቋንቋ መተርጎምና ማብራራት

ለኢትዮጵያ ማሕበረሰብ የተዘጋጀ አገልግሎት ሲሆን በሕክምና ሂደቱ ውስጥ በግል ድጋፍ ይሰጣል። ለሐኪማችን የሕክምና ችግራችንን እንዴት ማስረዳት እንዳለብን በግልጽ ማብራራትና የሕክምና ሠነዶችን ከዕብራይስጥ ወደ አማርኛ መተርጎም – ስሜትንና ምስጢራዊነትን በጠበቀና ባህላችንን ባማከለ ግንዛቤ።

የሕክምና ሠነዶችን ቀለል ባለ ቋንቋ መተርጎምና ማብራራት

ለኢትዮጵያ ማሕበረሰብ የተዘጋጀ አገልግሎት ሲሆን በሕክምና ሂደቱ ውስጥ በግል ድጋፍ ይሰጣል። ለሐኪማችን የሕክምና ችግራችንን እንዴት ማስረዳት እንዳለብን በግልጽ ማብራራትና የሕክምና ሠነዶችን ከዕብራይስጥ ወደ አማርኛ መተርጎም – ስሜትንና ምስጢራዊነትን በጠበቀና ባህላችንን ባማከለ ግንዛቤ።

የሕክምና ሠነዶችን ቀለል ባለ ቋንቋ መተርጎምና ማብራራት

ለኢትዮጵያ ማሕበረሰብ የተዘጋጀ አገልግሎት ሲሆን በሕክምና ሂደቱ ውስጥ በግል ድጋፍ ይሰጣል። ለሐኪማችን የሕክምና ችግራችንን እንዴት ማስረዳት እንዳለብን በግልጽ ማብራራትና የሕክምና ሠነዶችን ከዕብራይስጥ ወደ አማርኛ መተርጎም – ስሜትንና ምስጢራዊነትን በጠበቀና ባህላችንን ባማከለ ግንዛቤ።

ጥያቄዎችና መልሶች

ከጀማሪዎች እስከ ከፍተኛ ደረጃ ላሉ
አዎ፣ በቅድመ ምዝገባ በዙም ይሰጣል።
ለማብራሪያና ላሉበት ደረጃ ፈተና ወደ 053-791-4946 ይደውሉ።
የአማርኛ ዳራዎን በመጠቀም “የቅድመ እውቀት ትግበራ” ዘዴን እንከተላለን።
ትምህርቱ የሚቀረጽ ሲሆን ለድጋሜ እይታ ክፍት ነው።
በሣምንት ሦስት ጊዜ በቀን ደግሞ ለሁለት ሠዓታት ያህል ይሰጣል።
100%! ሁሉም ሠነድ ሙሉ በሙሉ በስሜት ጠባቂነትና ምስጢራዊነት ይያዛል።

የመረጃ ማዕከላችን

ተሣታፊዎች ስለ እኛ ምን ይላሉ?

TIKTOK

ላይቭ